søndag 10. november 2013

Plot to assassinate G7PF leaders foiled

ESAT News  November 09, 2013

An assassination plot to kill Andargachew Tsige, the Secretary General of Ginbot 7 Movement and the leaders of Ginbot 7 Popular Force (G7PF) has been foiled. The operation was masterminded by Getachew Assefa, Head of Ethiopia’s National Intelligence and Security Service (NISS) and Tsegaye Berhe, the Prime Minister’s Security Advisor.

According to the Popular Force, Muluken Mesfen, who has been sent with a mission of killing the selected individuals has been under the surveillance of the Force since he came to join the Force. The Intelligence Section of the G7PF has been recording all the telephone conversations that Muluken was having with the Ethiopian government’s spy chiefs.

According to the retrieved phone conversations, the assassination operation named ‘Woyane-O-Millennium’ was set to be executed on November 9, 2013. The selection of the date was made in connection with the graduation event that the Force was set to hold for its new members.

The Operation to kill leaders of the Force and officials of the Eritrean government was thwarted when the assassin, Muluken Mesfin, was taken into custody by the Force.

mandag 4. november 2013

ፊን ፊሸር ሰላዩ ቫይረስ

ኢትዮጵያ

ፊን ፊሸር የተባለ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም በዓለም 25 ሀገሮች ዉስጥ መሠራጨቱንና መንግስታቱም የገዛ ዜጎቻቸዉን ለመሠለል እንደሚጠቀሙበት አንድ ጥናት አመለከተ። ኢትዮጵያ ዉስጥም በሠፊዉ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን ጥናቱ ይፋ አድርጓል።
የኢንተርኔት ቫይረሱ ኮምፕዩተር ዉስጥ ከገባ ግለሰቦች በኮምፕዩተራቸዉ ላይ የሚያደርጉትን የፅሁፍ የድምፅና የምስል የመልዕክት ልዉዉጦች ወደዋና መረጃ ማሰባሰቢያዉ ማዕከል ይልካል። ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች RSF ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚደረገዉን ቁጥጥር አስመልክቶ የተጠቀሰዉ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ሥራ ላይ መዋሉን ጥናቱን ጠቅሶ ለዶቼ ቬለ መግለፁን ዘግበናል። ዶቼቬለ ስለጉዳዩ የጠየቃቸው የኢትዮ ቴሌኮም የኮምንኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሂም አህመድ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠቀሰው ፕሮግራም እንደማይገለገል በስልክ ተናግረዋል። አቶ አብዱራሂም ስለጥናቱ ውጤት እንደማያውቁ ገልፀው ሆኖም ፊን ፊሸር የተባለው የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ላይ ውሏል መባሉን ከዕውነት የራቀ ሲሉ አጣጥለውታል።
ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት RSF በያዝነዉ ሳምንትባወጣዉ የኢንተርኔት ቁጥጥርን የሚመለከት ዘገባ አምስት ሀገሮችን የኢንተርኔት ጠላት ሲል ፈርጇል። የሶርያ፤ ቻይና፤ ኢራን፤ ባህሬን እንዲሁም የቬትናም መንግስታት የኢንተርኔት መረጃዎችን ለመቆጣጠር ከሚሰነዝሩት የድረገፅ ጥቃት በተጨማሪ ዜጎችን ለመሰለል የግለሰቦችን የኢሜል መረጃ የሚያጠምዱ ፕሮግራሞችን በመጠቀም ግንባር ቀደም ተብለዋል። ከበርካታ ሀገሮች እነዚህ አምስቱ የተመረጡትም ለኢንተርኔት ቁጥጥሩ የሚጠቀሙበት ቴክኒዎሊጂ መራቀቅና በዚህ ስለላ መሠረትም ጋዜጠኞችና ዜጎቻቸዉን በማሰራቸዉ እንደሆነ የRSF የዘመናዊ መገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ተመራማሪ ግሬግዋ ፑዤ ገልፀዋል። በተለይም ቻይና የኤሌክትሮኒክ መከላከያዋ ከዓለም ምናልባትም የረቀቀ ተብሎ ሲገመት ይህንኑ ቁጥጥሯን ለማጠናከር የግል ኢንተርኔት ኩባንያዎች ዜጎቿን ለመሰለል የሚረዱ ስልቶችን እንዲያቀርቡላት ማድረጓም ተገልጿል። ኢራን በበኩሏ የራሷን «ሃላል ኢንተርኔት» በሚል አቋቁማ የኢንተርኔት መረጃ ቁጥጥሯን አጠናክራለች። RSF የተራቀቀ ቴክኒዎሎጂን ሳይኖራቸዉ አምባገነን መንግስታት ዜጎቻቸዉን ለመሰለል እንደማይችሉ በማመልከት ለመጀመሪያ ጊዜ ተባባሪ የኢንተርኔት ጠላቶች ሲል የመሰለያ ፕሮግራሞችን የሚሰሩና ለሀገራቱ የሚያቀርቡ ድርጅቶችንም ስም አጋልጧል። ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት ዜጎቻቸዉን በኢንተርኔት መረጃ ልዉዉጥ ሳይቀር እንዲቆጣጠሩና እንዲሰልሉ ስልቱን እያስተካከሉ የሚያቀርቡትን አምስት የግል ኩባንያዎችም የዘመኑ «ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች» ሲል RSF ወቅሷል።
ኢትዮጵያ ዉስጥ በርከት ያሉ ድረ ገፆች መነበብ እንደማይችሉ ተደጋግሞ የተገለፀ ጉዳይ ነዉ፤ መንግስት በበኩሉ ወቀሳዉን ቢያስተባብልም። የጥናቱ ተባባሪ ፀሐፊ ግሬግዋ ፑዤ ከአምስቱ ሀገሮች ተርታ በዘገባዉ ኢትዮጵያ ያልተጠቀሰችዉ የኢንተርኔት አገልግሎቱ እንደአምስቱ ሀገሮች የተስፋፋ ባለመሆኑ እንደሆነ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል። ያ ማለት ግን ድርጅታቸዉ ክትትል አላደረገም ማለት አይደለም፤
«ባለፈዉ ዓመት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምን እንደተደረገ እየተካተልን ቆይተናል። ማለትም TOR የተሰኘዉ ስልት ተዘግቷል፤ የሰዎች ኢሜይል ልዉዉጥ እየሰበረ የሚበረብረዉ DPI የተሰኘዉ ፕሮግራምም ስራ ላይ መዋሉን እናዉቃለን፤ ዛሬ ደግሞ ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ከቶሮንቶ አንድ ዘገባ አዉጥቷል፤ ያም ኢትዮጵያ ዉስጥም አንድ የግለሰቦችን የኮምፕዩተር መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም መጠቀም መጀመሩን ይገልፃል። ተቋሙ ዛሬ ይፋ ባደረገዉ ዘገባ ፕሮግራሙ ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚካሄደዉን ቁጥጥር የሚያረጋግጥ መረጃ አካቷል።»
ግሬግዋ ፑዤ የጠቀሱት ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ይፋ ያደረገዉ ዘገባ የግለሰቦችን መረጃ የሚያጠምደዉ የኢንተርኔት ፕሮግራም ፊን ፊሸርስ እንደሚባል ይገልፃል። እንደዘገባዉም ኢትዮጵያ በተለይም ከተቃዉሞ ፖለቲካ ቡድኖች ጋ ግንኙነት ያላቸዉ ግለሰቦችን ለመከታተል ትጠቀምበታለች።
ኩባንያዉ ይህን የግለሰቦችን የኢንተርኔት መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ያዘጋጀዉ የግንቦት ሰባት አባላትን ፎቶዎች በመጠቀም እንደሆነም ዘገባዉ በመዘርዘር ምስሎቹን ያሳያል። ግሬግዋ ፑዤ፤
«ባለፈዉ የበጋ ወቅት ሲቲዚን ላብ ፊን ፊሸር የተሰኘዉ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ዉስጥ ሥራ ላይ መዋሉን ደረሰበት። የግንቦት ሰባትን «ስሙን በትክክል ብየዉ እንደሁ አላዉቅም» ምስል የያዘዉ ይህ ህገወጥ ፕሮግራም በርካታ የተቃዉሞ ፓርቲ አባላት በኢሜል አድራሻቸዉ እንዲደርሳቸዉ ተደረገ። እናም ይህ ምስል ትክክለኛ መልዕክት የያዘ ሳይሆን ያ መረጃ የሚያጠምደዉ ፕሮግራም ነዉ። ይህን ፕሮግራም አንዴ ኮምፕዩተርሽ ዉስጥ ከገባ ወደማዘዣዉ ኮምፕዩተር መረጃዎችን በሙሉ እየቀዳ ይልካል። ይህ ነገር ኮፕዩተርሽ ዉስጥ ካለ እያንዳንዷ የምትፅፊያት ነገር ፕሮግራሙን ወደላከዉ አካል ይሸጋገራል።» እሳቸዉ እንደሚሉትም ሲቲዚን ላብ ባደረገዉ ክትትል የግለሰቦችን መረጃ እየቀዳ የሚልከዉ ህገወጥ ፕሮግራም ትዕዛዝ አስተላላፊ የኮምፕዩተር መረጃ ማከማቻ የሚገኘዉ እዚያዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን ደርሶበታል። ኢትዮጵያ ዉስጥ በኢንተርኔት ላይ የሚከናወነዉን ጥብቅ ቁጥጥር እና ስለላ አስመልክቶችም ሲቲዚን ላብ ይፋ ያደረገዉን አዲስ መረጃ በማካተት ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ዘገባ ይፋ እንደሚያደርግም ከወዲሁ ጠቁመዋል።
አበበ ፈለቀ
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሰ

ወይዘሮ አዜብ መስፍን የፓርቲ መልቀቂያ አቀረቡ


ወይዘሮ አዜብ መስፍን የፓርቲ መልቀቂያአቀረቡ: ተቀባይነት አላገኘም::
ሕወሓት ለወይዘሮ አዜብ ስልጣን በመስጠት በስልት ልታጠምዳቸው ነው::

"ለእኔ ስም የሚያወጡልኝ ተቃዋሚዎች ሳይሆኑ የሕወሓት ሹሞች ናቸው::" የሚሉት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ባለቤት የሆኑት እና የሙስናዋ ወይዘሮ በመባል የሚታወቁት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ለፓርቲያቸው ያቀረቡት የፖለቲካ በቃኝ ማመልከቻ ተቀባይነት ማጣቱ ሲገለጽ የሕወሓት ከፍተኛ ሰዎች ወይዘሮ አዜብን ለማጥመድ በሚያስችል ስልጣን ላይ ሊያስቀምጧቸው እንዳሰቡ ምንጮቹ ጠቁመዋል:: የደህንነት ሹሙ አቶ ጌታቸው በወይዘሮ አዜባ ጋር በዋዛ አንላቀቅም በማለት ቂም በቀላቸውን ሊወጡባቸው ይችላሉ የሚል ግምቶች በሕወሓት አከባቢ እየተነገሩ ነው::

ለወይዘሮ አዜብ የታሰበው ስልጣን የትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በስልት ከፖለቲካ ለማፈግፈግ እና ለመልቀቅ ከአገር ለመውጣት እንደማይቻል ተነግሯቸዋል:: ወይዘሮ አዜብ በድጋሚ ማመልከቻ ማቅረባቸው እንደማይቀር የጠቆሙት ምንጮቹ ምንኛውም ስልጣን ቢሰጣቸው በአዲስ አበባ መስተዳደር ምክር ቤት ውስጥ አባል ሆነው የመቀጠል ፍላጎት እንዳሌላቸው በግልጽ ተናግረዋል::ባልቤቴ ከሞተ በኋላ በሕወሓት ተገፍቻለሁ የሚሉት ወይዘሮ አዜብ ምንም ነገር ሊመቻቸው እንዳልቻለ እና ስለ እሳቸው ውስጥ ለውስጥ የሚነዙ ፕሮፓጋንዳዎች እያበሳጯቸው እንደሆነ ተናግረዋል በተጨማሪም ለእኔ ስም የሚያወጡልኝ ተቃዋሚዎች ሳይሆኑ የሕወሓት ሹሞች ናቸው ሲሉ አማረዋል::

ምንሊክ ሳልሳዊ.
“የእስክንድር ነጋ ጋዜጣ ቅንጅትን ወደተሳሳተ አቅጣጫ ገፍቷል”አቶ ልደቱ አያሌው በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጎልተው መውጣት የጀመሩት በ1990ዎቹ ሲሆን፣ ከምርጫ 97 ዋዜማ አንስቶ አነጋጋሪነታቸው በእጅጉ ጨምሯል፡፡ ከሁለት ዓመት የእንግሊዝ ቆይታ በኋላ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሱት አቶ ልደቱ አያሌው ጋ፣ የሎሚ መፅሔት አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው አሰናድቶታል፡-

የወያኔ ዘረኝነት ፖሊሲ ትግርኛ የማይናገሩ ኢትዮጵያዉያንን የበይ ተመልካች እያደረገ መሆኑን የግንቦት 7 ጥናታዊ ሪፖረት አጋለጠ!



የወያኔ ዘረኝነት ፖሊሲ ትግርኛ የማይናገሩ ኢትዮጵያዉያንን የበይ ተመልካች እያደረገ መሆኑን የግንቦት 7 ጥናታዊ ሪፖረት አጋለጠ
oct31,2013
የወያኔ ዘረኝነት ፖሊሲ ትግርኛ የማይናገሩ ኢትዮጵያዉያንን የበይ ተመልካች እያደረገ መሆኑን የግንቦት 7 ጥናታዊ ሪፖረት አጋለጠ


ባለፈዉ ሳምንት ኢትዮ ተሌኮም ዉስጥ ስር እየሰደደ የመጣዉን የወያኔ ዘረኝነት በመረጃ በተደገፈ ጥናታዊ ዘገባ ለህዝብ ይፋ ያደረገዉ የግንቦት 7 የአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ ዘርፍ በዛሬዉ ዕለት ደግሞ በተመሳሳይ ደረጃ አደረጃጀቱን፤ አወቃቀሩንና የሰዉ ኃይል አመዳደቡን ለአንድ አመት ሙሉ በቅርበት የተከታተለዉን የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺንን ጥናታዊ ዘገባ ለኢትዮጵያ ህዝብ ይፋ አድርጓል። ለኢትዮጵያ ከባድ እንዱስትሪ ግንባታ መሠረት ለመጣልና በአገሪቱ ኮንስትራክሺን እንቅስቃሴ ከፍተኛ ሚና እንዲጫወት ታስቦ የተዋቀረዉ የብረታብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን የኢትዮጵያ መሆኑ ቀርቶ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪ የህወሀት መኮንኖች እጅ መግባቱን ያጋለጠዉ የኸዉ የግንቦት 7 ጥናት ኮርፖሬሺኑ ከዋና ዳይረክተር እስከ ተራ ቴክኒሺያኖች ስረስ የህወሀት አባል በሆኑ የትግራይ ተወላጆች ቁጥጥር ስር ወድቋል ብሏል። የጥናቱ ሙሉ ዘገባ እንደሚገተለው ቀርቧል።
መነቀል ያለበት ስር የሰደደ የወያኔ ዘረኝነት (ሙሉ ጥናቱን በPDF ከዚህ ላይ ዳውሎድ ማድረግ ይቻላል)
(በግንቦት 7 የአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ ዘርፍ የተጠናና የተዘጋጀ)
ዘረኛዉ የወያኔ ስርአት የኢትዮጵያን ህዝብ ለጥቂት አመታት ኢትዮጵያዊያንን ባሰረና በገደለ ቁጥር ገንዘብ የሚሰጡትን አለም አቀፍ ድርጅቶችና አርዳታ ሰጪ አገሮች ደግሞ 21 አመት ሙሉ ካታለለበት መንገድ አንዱ የፌዴራል ስርአት መስርቼ ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር አደረኳት የሚለዉ ባዶ አባባሉ ነዉ። ይህንን ተጋልጦ እርቃኑን የቀረ አባባል የኢትዮጵያ ህዝብ ተገንዝቦ ወያኔን መታገል ከጀመረ ቆይቷል፤ ዋና ዋናዎቹ እርዳታ ለጋሾችም ቢሆኑ ለኢትዮጵያ ህዝብ ደህንነት ግድ የሌለዉ ወያኔ ወጣቶቻችንን እየገበረ ጥቅማቸዉን ስለሚያስከብርላቸዉ ነዉ እንጂ ወያኔ እንኳን እየደገፉ እርዳታ የሚሰጡት በአንድ ተርታም አብረዉ ለመቀመጥ የማይመች የእኩዮች ስብስብ እንደሆነ ካወቁ ቆይቷል።
ህወሀት በፌዴራል ስርአቱ ዉስጥ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት ነዉ ብሎ በሚጠራዉ ፓርላማ ዉስጥ ያለዉ መቀመጫ 8 ብቻ ነዉ። እዚህ ፓርላማ ዉስጥ የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ የሚለዉ ህወሀት ነዉ፤ ትግራይ ደግሞ ኢትዮጵያ ዉስጥ አንድ ክልል ናት። የተቀሩት 8 ክልሎች በዚህ የእኩልነት ምልክት በሆነዉ ፓርላማ ዉስጥ ያላቸዉ የመቀመጫ ብዛት 569 ነዉ። ሆኖም በወያኔ መንደር የፖለቲካ ስልጣን ምንጭ ህዝብ ሳይሆን ጠመንጃ ነዉና ወያኔ ፓርላማዉ ዉስጥ 8 ወንበር ብቻ ይዞ 569 ወንበር ያላቸዉን የኦሮሚያን፤ የአማራን፤ የደቡብ ክልልንና የተቀሩትን አምስት ክልሎች እንደ መኪና ይነዳቸዋል። የየክልሉን መሪ ይሾማል፤ ይሽራል ወይም የማይስማማዉን የክልል ባለስልጣን ያስራል። ፓርላማዉ ዉስጥ አንድ መቶ ሰባ ስምንት፤ አንድ መቶ ሰላሳ ስምንትና አንድ መቶ ሀያ ሦስት መቀመጫ ያላቸዉ የኦሮሚያ፤ የአማራና የደቡብ ክልል ፓርቲዎች በራሳቸዉ ጉልበትም ሆነ ህልዉና ስለሌላቸዉ አንዱ ከሌላዉ የበለጠ ስልጣን ወይም ሹመት ለማግኘት አንጋጥጠዉ ወደ ላይ የሚመለከቱት ህወሀትን ነዉ።
ለመሆኑ ወያኔ የፌዴራል ስርዐት መስርቼ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት አረጋገጥኩ ሲል ምን ማለቱ ነዉ? እኩልነቱ የፖለቲካ ነዉ የኤኮኖሚ? ወይስ በየአመቱ ህዳር ወር ላይ የፌዴራልዝም ቀን ሲከበር እንደምናየዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት የተረጋገጠዉ በዘፈን ብቻ ነዉ? የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስርዐት ከላይና ከታች የሚቆጣጠረዉና ይህንኑ የፖለቲካ ስርአት የሚደግፍ የኤኮኖሚ መዋቅር ዘርግቶ የአገራችንን ኃብት የሚቦጠብጠዉ ህወሀት ብቻ ነዉና የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ተረጋገጠ የሚባለዉ አባባል ከተራ የቃላት ድርደራ ዉጭ ሌላ ምንም ትርጉም የለዉም።
አፄ ቴዎድሮስን እንደ ልጅነት ሞዴሉ የሚመለከተዉ ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማሪያም የመጀመሪያዉን የኢትዮጰያ ዘመናዊ ወታደራዊ እንጂኔሪንግ ተቋም ሲመሰርት ስሙን “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ ነበር የሰየመዉ። ስያሜዉ የአፄ ቴዎድሮስ ስራና ስም ህያዉ ሆኖ እንዲኖር ለማድረግ የተደረገ ሙከራ እንደነበር ግልጽ ነዉ። የኢትዮጵያን የቀድሞ መሪዎች በጅምላ የሚዘልፈዉ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ከአንዲት የአገር ዉስጥ ጋዜጠኛ ጋር ባደረገዉ ቃለ ምልልስ አፄ ቴዎድሮስ ጋፋት ላይ ያሰሩትን መድፍና መንግስቱ ኃ/ማሪያም “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ የሰየመዉን ወታራዊ ተቋም አስመልክቶ ሁለቱንም መሪዎች ሲያንቋሽሽ ተደምጧል። የሚገርመዉ ዛሬ ወያኔ የብረታብረት እንጂኔሪንግ ኮረፓሬሺን ብሎ የሚጠራዉ ግዙፍ የሲቪልና ወታደራዊ እንዱስትሪ ተቋምና በዚህ ተቋም ዉስጥ የሚገኙ ዋና ዋና ፋብሪካዎች ደርግ “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ የጀመራቸዉ የከባድ እንዱስትሪ ጅምሮች ናቸዉ። በ1970ዎቹ አጋማሽ ላይ “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ስራዉን ሲጀምር የፋብሪካዉ ሀላፊዎች፤ እንጂኔሮች፤ የመምሪያ ሀላፊዎችና ቴክኒሺያኖች የስራ ዕድል የሚያኙት የትምህርት ደረጃቸዉ፤ ችሎታቸዉና የሰራ ልምዳቸዉ ብቻ እየታየ ነበር፤ ወይም ትግርኛ ስለተናገረ ስራ የሚከለከል አማርኛ፤ ኦሮምኛ ወይም ሌላ ቋንቋ ስለተናገረ አድሎ የሚደረግለት ዜጋ አልነበረም። ዛሬ ወያኔ ከደርግ ስርአት ተረክቦ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ብሎ በሰየመዉ እንዱስትሪ ዉስጥ አብዛኛዉን የሀላፊነት ቦታ የያዙ ሰዎች ለቦታዉ የበቁት በስራ ልምዳቸዉና ችሎታቸዉ ሳይሆን የተወለዱበት ዘርና የሚናገሩት ቋንቋ እየታየ ነዉ። ወታራዊዉ አምባገነን ደርግም ሆነ ወያኔ ይህንን እንዱስትሪ የወደፊቱ የኢትዮጵያ ከባድ እንዱስትሪ ዘርፍ መሰረት ይሆናል የሚል ራዕይ ነበራቸዉ። ልዩነታቸዉ የእንዱስትሪዉ አስፈላጊነት ላይ ሳይሆን እንዱስትሪዉን ማን ይቆጣጠረዋል የሚለዉ ጥያቄ ላይ ነዉ። ደርግ በሱ መሪነት ለማንም ችሎታ ላለዉ ኢትዮጵያዊ የእንዱስትሪዉን በር የከፈተ ሲሆን ወያኔ ግን እንዱስትሪዉ እንዳለ በአንድ ዘር ቁጥጥር ስር እንዲገባ አድርጓል። ደርግም ወያኔም አምባገነኖች ስለሆኑ አንዱስትሪዉን ከህዝብ ቁጥጥር ዉጭ አድርገዉታል፤ ወያኔ ግን ከአምባገነንም የጎሳ አምባገነን ስለሆነ ይህንን ትልቅ እንዱስትሪ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪዎች ቁጥጥር ስር አድርጎታል።
ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ባለለፉት ሦስት አመታት ይህንን ወያኔ ገነባሁ የሚለዉን የፌዴራል ስርአትና በስርአቱ ዉስጥ የተለያዪ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የሚጫወቱትን ሚና በመረጃ አስደግፎ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ አቅርቧል። የዛሬ ሁለት አመት ግንቦት ሰባት በኢትዮጵያ መላከያ ሰራዊት ዉስጥ የተዘረጋዉን የወያኔ የዘረኝነት መረብ ከሰሞኑ ደግሞ የኢትዮቴሌኮምን የዘረኝነት አደረጃጀት በመረጃ በማስደገፍ ለህዝብ ማቅረቡ ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮረፓሬሺንን የዘረኝነት አደረጃጀትና በዚህ አደረጃጀት ዉስጥ ማን ምን እንደሆነ ያጣናዉን የጥናት ዉጤት በመረጃ አስደግፎ ያቀርባል። ግንቦት ሰባት ሃያ አራት ሰአት ሙሉ የሚከታተሉትን የወያኔ የደህንነት ሰራተኞች ከበባ ጥሶ የወያኔን ዘረኝነት የሚያጋልጡ መረጃዎችን ከራሱ ከወያኔ ጓዳ እየጎተተ አዉጥቶ ለህዝብ የሚያቀርበዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔን ዘረኝነት አያውቀዉም በሚል አስተሳሰብ አይደለም። ግንቦት ሰባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ የፈጠረዉ ከፍተኛ የመረጃ ጉድለት አለ ብሎ ያምናል፤ስለሆነም ህዝቡ የወያኔን ዘረኝነት ቢረዳም መጠኑን፤ስፋቱንና ጥልቀቱን በሚገባ ላያዉቅ ይችላል ብለን እናምናለን። በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በየቀኑ ደሙን እንደ መዥገር የሚመጠዉን ወያኔን የመሰለ የጀርባ ላይ አጥንት ተሸክሞ መኖር የለበትም ብለን ስለምናምን ህዝብን ለትግል ከምናዘጋጅበትና ከምናነሳሳባቸዉ መንዶች ዉስጥ አንዱ እንደዚህ ህዝብ በገዛ አገሩ “እኩል አደረግንህ” ብለዉ በሚነግሩት ከሀዲዎች ቅኝ አገዛዝ እየተገዛ መሆኑን በማሳወቅ ነዉ።
ባለፈዉ ሳምንት የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ዋና ዳይረክተር ብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘዉ ፓርላማ ዉስጥ ተገኝቶ የኮርፓሬሺኑን የሁለት አመት የስራ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ኮርፓሬሺኑ የግል ባለኃብቶችን አያሳትፍም እንዳዉም እያቀጨጫቸዉ ነዉ፤ ለሙስና የተጋለጠ ነዉ፤ ደግሞም አብዛኛዉ የኮርፖሬሺኑ ሰራተኛ የመከላከያ ሰራዊት አባል ነዉና ይህ አሰራር ሠራተኞችን ለማስተዳደር አስቸጋሪ አይሆንም ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዉለት ነበር። የግሉን ዘርፍ መቅጨጭ በተመለከተ ኢትዮጵያ ዉስጥ ቀድሞዉንም ቢሆን “የወያኔ ዘርፍ” እንጂ የግል ዘርፍ የሚባል ነገር የለምና ጥያቄዉ መቅረብም አልነበረበትም። ሙስናም ቢሆን የወያኔ ስርዐት ዋናዉ መገለጫ ባህሪይ ስለሆነ ወያኔ እስካልተወገደ ድረስ ሙስና “ሙስናን እናጠፋለን” ስለተባለ ብቻ የሚጠፋ ነገር አይደለም። ግንቦት ሰባትን እጅግ በጣም ያሳዘነዉና ያስገረመዉ ነገር ያንን ወያኔ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት ነዉ ብሎ የሚናገርለትን ፓርላማ ያስጨነቀዉ (ተጨንቆ ከሆነ) የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን በአንድ አናሳ ብሔረሰብ ሙሉ ቁጥጥር ስር መዉደቁ ሳይሆን አብዛኛዉ የኮርፖሬሺኑ ሰራተኞች የመከላከያ ሰራዊት አባላት መሆናቸዉ ነዉ። በእርግጥ የአንድ ትልቅ ኮርፖሬሺን ሰራተኞች በአብዛኛዉ የጦር ሠራዊት አባላት ሲሆኑ የአሰራርና የአስተዳደር ችግር መፈጠሩ አይቀርም፤ ሆኖም የሠራዊቱ ታማኝነት ለህዝብ ታዛዥነቱ ደግሞ ለህገ መንግሰስቱ ብቻ ቢሆን ኖሮ ይህ ችግር በቀላሉ የሚወገድ ችግር ይሆን ነበር።
የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን በአምሰት አመቱ የእድገትና የትራንስፎርሜሺን ፕላን ዉስጥ የሚጫወተዉን ቁልፍ ሚና ፓርላማዉ በሚገባ የሚገነዘበዉ ይመስለናል፤ ታዲያ ይህ በአገር እድገት ዉስጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወተዉ ኮርፖሬሺን ሙሉ በሙሉ በአንድ ብሔር ቁጥጥር ስር ሲወድቅ ምነዉ የብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት የሆነዉ ፓርላማ አፉን ዘግቶ ተመለከተ? ፓርላማዉን ይበልጥ የሚገድደዉ የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ በአንድ አናሳ ብሔረሰብ ሙሉ ቁጥጥር ስር ሆኖ ሌሎቹ ብሔረሰቦች ተመልካች ሲሆኑ ነዉ ወይስ የአንድ ኮርፖሬሺን ሰራተኞች በአብዛኛዉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲሆኑ ነዉ? ለመሆኑ የወያኔ ዘረኝነት በኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ዉስጥ ምን ያህል ዘልቆ ገብቷል? የኦሮሞ፤ የአማራ፤ የሶማሌ፤ የሲዳማና ሌሎቹም ብሔር ብሔረሰቦች በዚህ ለአገር እድገት ቁልፍ በሆነ ኮርፖሬሺን ዉስጥ የሚጫወትቱት ሚና ምን ይመስላል?
የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን በአስራ አንድ መምሪያዎችና ጽ/ቤቶች የተዋቀረ ሲሆን በስሩ አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱስትሪዎቸን ያስተዳድራል፤ ይህ ሪፖርት እስከተጠናቀቀበት ቀን ድረስ ቁጥራቸዉ በዉል ተለይቶ ባይታወቅም አስራ ሦስቱ እንዱስትሪዎችም እያንዳንዳቸዉ በስራቸዉ ብዙ ፋብሪካዎችንና የማምረቻ ተቋሞችን ያቀፉ ናቸዉ። የኮርፖሬሺኑን አስራ አንድ ትላልቅ መምሪያዎችና አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱሰትሪዎች በዋና ሀላፊነት፤ በዳይረክተርነተና በምክትል ዳይረክትርነት የሚመሩ 29 የከፍተኛ አመራር አባላት አሉ። ከእነዚህ 29 ከፍተኛ አመራር አባላት ዉስጥ 69 በመቶዉ ወይም ሃያዉ ህወሀት ሆን ብሎ ያስቀመጣቸዉ ትግርኛ ተናጋሪ የሆኑ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸዉ።በዚህ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ያላቸዉ ቦታ 31 በመቶ ወይም ከእያንዳንዳቸዉ በቅደም ተከተል ሦስትና ስድስት ሰዎች ብቻ ሲሆን ከተቀሩት አምስት ክልሎች በዚህ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የተመደበ አንድም ሰዉ የለም። ኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ እንዱስትሪ ለመገንባት በሚደረገዉ ጥረት ዉስጥ ከፍተኛዉን ሚና ይጫወታል የሚባለዉ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን በሲቪልና ወታራዊ መምሪያዎች ተከፋፍሎ የተዳራጀ ሲሆን በስሩ አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱስትሪዎች ይገኛሉ። እነዚህን እንዱስትሪዎች በማስተዳደሩ በኩል የብሔር ብሔረሰቦችን ድርሻ ወይም ኮታ ስንመለከት ከአስራ ሦስቱ እንዱስትሪዎች ዘጠኙን የሚያስተዳድሩት የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። በኮርፖሬሺኑ ዉስጥ ከፍተኛ ስልጣን ከተሰጣቸዉ የትግራይ ተወላጆች ዉስጥ እነ ብረጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘዉ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን ዋና ዳይረክተር ፤ ኮ/ል ተከስተ ኃ/ማሪያም በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ፕሮዳክሺን ግንባታ ሀላፊ ፤ ኮ/ል ፀጋሉ ኪሮስ በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ወታደራዊ ምርቶች ሀላፊ ፤ ኮ/ል ሙሉ ወ/ሰንበት በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ፕሮጀክቶች አስተደዳደር ሀላፊ፤ሻምበል ካህሳይ ክሽን የምርመራና ልማት ዳይረክተርና ሻምበል ገ/ስላሴ ገ/ጊዮርጊስ የአቅም ግንባታና ስልጠና ማዕከል ዳይረክተርን የመሳሰሉ የህወሀት ታጋይ መኮንኖች ይገኙበታል።
ከትግራይ ዉጭ ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔሰቦች በብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን እንዱስትሪዎች ዉስጥ ከፍተኛ የሀላፊነት ደረጃ ባለዉ የአመራር ቦታ ላይ የመቀመጥ ዕድል ያገኙ ኢትዮጵያዉያን ቁጥር አራት ብቻ ነዉ። ይህ ጥናት የተጠናዉ ከ2004 እስከ 2005 ዓም ባለዉ የአንድ አመት ግዜ ዉስጥ ነዉ። በ2004 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ 90 ሚሊዮን አንደሚሆን የተገመተ ሲሆን ከዚህ ቁጥር ዉስጥ በትግራይ ክልል 5.4 ሚሊዮን ህዝብ በተቀሩት ስምንት ክልሎች ደጎሞ 84.6 ሚሊዮን ሀዝብ ይኖራል ተብሎ ተገምቷል። ይህ ጥናት በዋናነት የሚያመለክተዉ በዋና ዋና የሀላፊነት ቦታ የተቀመጡትን ግለሰቦችና ግለሰቦቹ የመጡበትን ብሔር ስለሆነ ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺንን የሰዉ ኃይል ምደባና የደረጃ እድገትን ጠለቅ ብለን ስንመለከት አብዛኛዎቹ እንጂኔሮችና ቴክኒሻኖች የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ፤ የደረጃ እድገትን በተመለከተም ከሌሎች ሰራተኞች ጋር ሲነፃፃር በፍጥነት የደረጃ እድገት የሚያገኙት እነዚሁ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። ይህ ደግሞ በአጋጣሚ የሆነ ነገር ሳይሆን ወያኔ በረሀ ዉስጥ እያለ አቅዶት ባለፉት ሃያ አመታት በስራ ላይ ያዋለዉ የረጂም ግዜ እቅድና ዝግጅት ዉጤት ነዉ። ለምሳሌ ወያኔ ትግራይ ዉስጥ ኤም አይ ቲ ወይም የመቀሌ ቴክኖሎጂ እንስቲቲዩት ብሎ የሚጠራዉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም ተቀብሎ የሚያስተምረዉ የትግራይ ተወላጆችን ሲሆን ከዚህ ተቋም የሚመረቁ እንጂኔሮችና ተክኒሺያኖች ናቸዉ በኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን የሚሊታሪ ክንፍና በኢትዮቴሌኮም የስለላ ተቋሞች ዉስጥ ተመድበዉ ከፍተኛ የስለላ ስራ የሚሰሩት።
ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝና አገር ዉስጥና በዉጭ አገር የሚገኙ ቡችሎቹ የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ድርጅቶች በተለይ በዳያስፖራ ዉስጥ የሚገኘዉን ለእናት አገሩ ተቆርቋሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በጅምላ “የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች” እያሉ ለአመታት ሲዘልፉን ኖረዋል። የፖለተካ ትግላችን አላማና ግብ ከጥላቻ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለዉ ቢሆንም – ለመሆኑ ይህንን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተና አንዱን አለቃ ሌላዉን ተላላኪ፤ አንዱን የሚሾም ሌላዉን የሚሽር፤ አንዱን አብልቶ የሚያጠግብ ሌላዉን የበይ ተመልካች የሚያደርግ፤ አንዱን የአገር መሪነት ቦታ ተረካቢ ሌላዉን ኮብልስቶን ድንጋይ ጠራቢ የሚያደርግ ስርዐት የሚወድ ማን አለ? ይህንን በንጹህ ዜጎች ደም እጁ የቆሸሰና ያደፈ ዘረኛ ስርአት ዉደዱ የሚለንስ ማነዉ? በምድርም በሰማይም የከሰሩ እነ ሚሚ ስብሀቱን የመሳሰሉ የፖለቲካ ሴሰኞች ሊነግሩን እንደሚፈልጉት ትግላችን የትግራይ ወንድሞቻችንንና እቶቻችንን በመጥላት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን የትግላችን ብቸኛ አላማ ከትግራይ ወንድሞቻችን ጋር ሊያጋጩን የሚሞክሩትን የህወሀት ወንጀለኞች አስወግደን ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር ማድረግ ነዉ።



onsdag 23. oktober 2013

አብረን እንነሳ (ከማንደፍሮ መንግስቱ በርገን ኖርዌይ)

እውነት በተነወረበት ሀቅ በተገደፈበት ምድር

ሸፍጥ በነገሰበት ሀሰት በተሞሸረበት ሃገር

የህዝብ ጆሮ ሲራብ እውነታን ማወቅ ሲጠማ

ስውሩን ሲገለጥለት ክስተቱን እናደለ ሲሰማ

መብቱ ሳይደፍሩ ፍቃዱን ሳይከለክሉ

ሰብናውን ሳያሳንሱ ነፃነቱን ሳያጎሉ

እነሆ አውነታውን ስማና እውቀውና ፍረደን ቢሉ

በህዝብ ልብ ይከብራሉ በህዝብ አይን ይጎላሉ

እንጂማ መብቱን ቢሸራርፉ

ፈቃዱን ቢያጎድፉ

በፍላጎቱ ቢያሾፉ

አልጋው ተመቸ ብለው ቢቀብጡ

በኔ ይሁንቦ አይቀሬ ነው ወድቆ ለመላላጡ

ግና ዘመን እስኪመጣ

ብሩህ ቀን እስኪወጣ

እነሆ ሀቅ ላትደበቅ እውነት ወግጅ ላይሉ

ልክ እንደቀድሞ የውሸት ግዳይ ላይጥሉ

የተነገረው እንደተነገረው የተፈጠረው እንደተፈጠረው … የሀቅ ግነት የለውም እንዲሉ

የህዝብን እንባ የትውልድን መከራ

ጭቆናና መድሎ እንዲሁም የዘረኝነት ሴራ

አደባባይ የሚያወጣ ከወገናዊነት የጠራ

ለኢትዮጵያዊነት የሚሰራ

ኢሳት ተወልዶ የወገንን እንባ ሲያብስ ማየቱ

ሀቅን እየገለጠ የሀገርን ምጽንታ መስማቱ

ለምጡዋ ምላሽ ለእንባዋ ማበሻ ልጆቹዋ ሲበረቱ

ወገን ካለበት ተጠራርቶ አንድነቱን ሲያሳይ

በሃብቱ በገንዘቡ በእውቀቱ የድርሻወን ሲያረግ ያለከልካይ

ኢሳት እሳት ሆኖ ገለባውን ሲበላ

ሀሰት አመድ ሆኖ እውነት እንደ ወጋጋን ሲያቅላላ

ትግሉ ነዶ ግሞ

እንደ ገሞራ ግሞ

የነዲዱ ወገግታ ካድማስ ሞዶ ይታየኛል

የፀዳሉ ግርማ የትንታጉ ጩኸት ይሰማኛል

እናም ወገኔ ሃገር ረዳት በምትሻበት በእንዲህ አይነቱ ሰአት

የሰው ያለ እያለች በምትጣራበት ወራት

ወገኔ ሆይ ጆሮህንም ኪስህንም አትንፈጋት

ይልቁንስም ለንዲህ አይነቱ ጥሪ ለመከራ ጩኸቱዋ

ሁንላት አይዞሽ ባይ ሁንላት ረዴቱዋ

ለእውንት ለሚታገል ለህዝብ ድምጽ ከሚሰራ

ከጭቁኖች ልሳን ታገል ከኢሳት ጋራ

አንድ ላይ ተንስ ጨለማው ላይ አብራ፡
                                                                                                 

                                                    ኢትዮዽያ ለዘላለም ትኑር

mandag 21. oktober 2013

የተሞሉትን የሚተነፍሱ ጠቅላይ ሚኒሰትር



Ethiopian PM Hailemariam Desalegn on Al Jazeeraለሁለት  አስርተ አመታት በኢትዮጲያና  በህዝቦቿ ላይ ነግሶ በማን አለብኝነት አድራጊ ፈጣሪ ሆኖ በሁሉም ያገሪቱ አቅጣጫዎች ሰላማዊውን ህዝብ ለሞትና ለስደት እንዲሁም ለእስር ሲዳርግ የነበረው አምባገነኑ የህውሃት ዘረኛ ቡድን የመለስ ዜናዊ  ሞት ተከትሎ በይስሙላ ምርጫ ያስቀመጠው አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የዚሁ ዘረኛ ቡድን ደቀ መዝሙር ሆኖ በነሱ በመቃኘት ተፈጥሮአዊ ባህሬያቸውን ወርሶ አሁንም በሃገራችን  ስርዓቱ ካለው እኩይ ተፈጥሯዊ  ባህሪ አንፃር የናፈቅነውንና የተመኘነውን ነፃነትም ሆነ ለውጥ ሳይመጣ እነሆ ሌሎች ንፁሃን ሲገደሉና ሲሰደዱ እንዲሁም ሲታሰሩ አየን ሰማን፡፡
ለብዙሃን ዜጎች ህይወት መጥፋት፣ መሰደድና በየእስር ቤቱ መታጎር ተጠያቂ የሆነው አምባገነኑ የወያኔ ቡድን እንዲሁም ስርዓቱ  በተለይ ሃገር ሲያፈርሱ፣ ሲመዘብሩና ደሃውን የህብረተሰብ ክፍል ሲየፈናቅሉና በችጋር ሲቆሉ የነበሩት የህወሃት መስራቾች በዘፈቀደ ባገኙት አጋጣሚ እዚህ ምስኪን ህዝብ ላይ አፋቸውን ማላቀቃቸውን መዘባበታቸው የተለመደ ቢሆንም   የወያኔ ጠ/ሚንስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በተለያየ አጋጣሚ በስርዓቱ መገናኛ ቡዙሃን ቀርበው የሚሰጡት አስተያየትም ሆነ የሚናገሩት እጅግ የወረደና ስነምግባር የሌለው ዲስኩር ሰውየው በራሳቸው ሳይሆን ስርዓቱ እንደፈለገ እንደሚዘውራቸው ፍንትው አርጎ የሚያሳይ ነው፡፡
ጥቂት የማይባል የህብረተሰብ ክፍል ለዝች ዘመናትን በግፍና በመከራ ላሳለፈ ሃገርና ህዝብ የመጣል ተብሎ በታሰበው ወይም በመጣው አዲሱ መሪ ላይ ጭላንጭል ተስፋ ሰንቆ ቢቆይም  ተስፋ አሰቆራጭ ሁኔታ የተፈጠረው ብዙም ግዜ ሳይፈጅ መሆኑ ተስፋ አድርጎ የነበረውን ተስፈኛ አሁንም የመከራው ቀንበር መፈታት ሳይሁን አለመላላቱን  ያየነው አዲሱ  ጠ/ሚንስትር  ሃ/ማርያም ደሳለኝ ከሀ እስከ ፐ የሟች  ቅጂ መሆናቸው እየተስተዋለ ሲመጣ ነው፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ የወያኔ ስርዓት በዙሪያው የሚሰበስባቸውና ወደ ስልጣን የሚያስጠጋቸው ሰዎች ምን አይነት አመለካከትና ስብእና ወይም ሀገራዊም ሆነ ህዝባዊ ስሜት አላቸው ? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ሊቅ ወይም ነብይ መሆን የሚጠበቅብን አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም የህውሃት ወያኔ ቡድን ይችን ሃገር በገዛበት ሁለት አስርተ የግፍና የመከራ ዘመን ውስጥ በራሳቸው የሚተማመኑትን፣ በሃሳብ ደረጃ አምባገነኑን ስርዓት የሚሞግቱትን በተለይ ለሃገርና ለህዝብ የሚጠቅም ፅንሰ ሃሳብ የሚያንፀባርቁትን የሃገር ሃብት ምሁራን ሲገድል፣ ሲገፋና ሲያሳድድ በግፍ ሲያስር  ዘመን ማሳለፉ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በአመለካከት  የተለዩትን አብረውት በትግል ሜዳ የነበሩትንም ሁሉ  ሳይቀሩ  ሲያሶግድ፣ ሲያስርና ሲያሳድድ መኖሩ  በህይወት ያሉ የቀድሞ የህውሃት ሰዎች ምስክር ናቸው፡፡ ይህንን ከተረዳን አቶ ሃ/ማርያም ደሳለኝ  በዚህ ስርዓት ተመርጠው  እንዴት እዚህ ደረሱ የሚለውን ለማወቅ ከላይ እንደጠቀስኩት ነብይ መሆን አይጠይቅም፡፡
በሁለተኛ ደረጃ አቶ ሃ/ማርያም በአለም አቀፍ ማህበረሰብ ተፅእኖም  ይሁን ወያኔ የህዝብ ይሁንታ ለማግኘት ቁልፍ የሆኑ የስልጣን ቦታዎችን  ይዞ ከፊት አስቀድሞ መንበረ ስልጣኑን ቢሰጣቸውም  ምንም  የመወሰን አቅም  የሌላቸው ወያኔ ለሽፋን ያስቀመጣቸው መሆናቸውን ያየንባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው፡፡የሳቸውም በራስ ያለመተማመን መንፈስና የስብእናችው ጉዳይ ታክሎበት በይዘትም ሆነ በፅንሰ ሃሳብ የዘረኛው አምባገነን ስርዓት ቅኝት መሆናችው በተደጋጋሚ ከሚሰሩት ስራ ለማየት ችለናል፡፡  የእሳቸው እራሳቸውን ያለመሆን ችግር አንድም እርምጃ ወይም ውሳኔ ለይስሙላ በተሰጣቸው ስልጣን እንደማይፈፅሙ የሚያሳየን ብዙ ማሳያዎች ቢኖሩም ለአብነት ያህል አንዱን ልጥቀስ፡፡ ከወራት በፊት የአውሮፓ የፓርላማ የልኡካን ቡድን በኢትዮጲያ ውስጥ ያሉትን የህሊና እስረኞች በተለዪም ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፣ጋዜጠኛና መምህርት እርእዮት አለሙ፣ እንዲሁም ወጣቱን ፖለቲከኛ  አንዶለም አራጌና ሌሎችንም የፖለቲካ እስረኞች ለመጎብኘትና ስላለው ሁኔታ ከእስረኞቹ ተጨባጭ መረጃ ለማግኘት በህጋዊ መንገድ አዲስ አበባ በመገኘት በተያዘላቸው ፕሮግራም መሰረት እኚሁ የወያኔን ሹመኛ ጠ/ሚ ሃይለማርአም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው ስለመጡበት አላማና ተነጋግረው በማግስቱ በተያዘላቸው ፕሮግራም መሰረት እስረኞችን ለመጎብኘት ቃሊቲ ያመራሉ ሆኖም እዛ ያጋጠማቸው የማይታመን ነገር ነበር፡፡ የህንን የአውሮፓ ፓርላማ ልኡካን ቡድን የቃሊቲው እስር ቤት አዛዥ እንደማያቃቸውና የመጡበትንም ተልእኮ እንደማይፈፅሙ አስረግጦ ነግሮ ይመልሳቸዋል፡፡ ልብ በሉ ጠ/ሚ ታብይው እንኚህን ዲፕሎማት ተቀብሎ አሰተናግዿል ስለመጡበትም ጉዳይ ጠንቅቆ ያቃል እናም ይሁንታውን ሰቷቸዋል ሆኖም በአለቆቹ በህውሃት በኩል የልኡካን ቡድኑ ጉብኝት እንዲሰረዝ ሆነ፡፡ ይህ ማለት ጠ/ሚ ተብዬው በራሱ አንዳችም የመወሰን ስልጣን እንደሌለውና በጥቂት የስርዓቱ ሰወች እንደሚነዳ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
ሰውየው ኢትዮጲያንና ህዝቧን የሚመሩት  ከአለቃቸው በውርስ ባገኙት የሳቸው ባልሆን  ባህሪ ብቻ ሳይሆን ይችን ሃገር መዝብረው በደለቡና በሰቡ የህውሃት ሰዎች በርቀት መቆጣጠሪይ ስለሆነ  ከህዝብ ሳይሆን  ከነኚሁ የሃገርና የህዝብ ጠላቶች  ክብርና ሞገስ  ለማግኘት   ሆዳምና ከራሱ ባለፈ ስንዝር  የማያስብ  ጥርቅም በሞላበት ፓርላማ ተብይ ውስጥ በሙት መንፈስ  እየተመሩ  መኮረጅ የቻሉትን  ያህል  ሲተውኑ፣  ተልኳቸውን በድል ለመወጣት ሲወራጩና  ሲሳደቡ፣ እንዲሁም ህዝብ  ክብር የሚሰጣቸውን የህሊና እስረኞችንና የነፃነት ታጋዮችን  ሲዘልፉ፣ ከቃላት አጠቃቀምና አስተያየት ጀምሮ የሳችው ባልሆነ ስብእና  የሚያደርጉት ትእይንት  በሳችው ደረጃ ካለ   ከተማረና  ከዚህ ዘመን ስልጡን ሰው የሚጠበቅ አይደለም፡፡
ሰሞኑን በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የታየው የሰውየው ባህሪ ምንም ጠብ የሚል ነገር ያልተገኘበት እንደውም ባዶ ነታቸው የጎላበት ነበር፡፡ እንዳየነው አርቆ ከማሰበና ከብስለት ጋር ያልተዋሃደ እጅግ ተራና የወረደ መግለጫ ሰውየው የተሞሉትን ያህል እንደተነፈሱ የሚያሳይ ነው፡፡ ህገ- መንግስቱ  በሚፈቅደው መልኩ ያውም እጅግ በጣም በጠበበ ምህዳር ለመብት፣ ለነፃነት፣ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሕዝቡን ዘርፈ ብዙ ችግር አንስተው የሚታገሉትን የፖለቲካ ድርጅቶች በዚህ መንገድ መግለፅ አሁንም ወደፊትም በሕዝብ ሊነሱ የሚችሉ ዘርፈ ቡዙ ችግሮች ያለበት ስርዓት ለከት በሌለው ልቅነት በዚህ መጠን መመፃደቅ ሕዝብን ከመናቅና ከማዋረድ እንደማይተናነስና  ዋጋም እንደሚያስከፍል ከስነምግባር ውጪ የሆኑት ጠ/ሚ የገባቸው አይመስልም፡፡
ድል  ለኢትዮጲያ   ህዝብ !!  ሞት ለወያኔና  ለሆዳሞች!

fredag 18. oktober 2013

Systematisk tortur av politiske fanger i Etiopia


Opposisjonspolitikere, journalister og regimekritikere blir utsatt for systematisk tortur på en politistasjon i Addis Abeba, viser ny rapport.

  
Torturmetodene som brukes er blant annet slag mot kroppen med harde gjenstander og pisking. Fanger blir også hengt fra taket i svært smertefulle posisjoner.
Human Rights Watch-rapporten, som presenteres i dag, gir et detaljert bilde av mishandlingen som foregår i landets beryktede Federal Police Crime Investigation Sector. Politistasjonen, som er kjent under navnet Maekelawi, ligger i hjertet av hovedstaden Addis Abbeba.
Flere menneskerettighetsaktivister har tidligere meldt om grufulle forhold ved Maekelawi. Denne ferske rapporten har gått systematisk til verks og intervjuet 35 tidligere innsatte ved Maekelawi og deres familiemedlemmer.

- Sparket meg i munnen med støvelen

En tidligere innsatt har fortsatt arr etter torturen.
- De sparket meg i munnen med støvelen, og da mistet jeg fire tenner, sier han.
En annen beskriver hvordan han ble holdt i en smertefull posisjon og så slått.
- De tok av skoene og sokkene mine og plasserte en pinne bak knærne mine. Så rullet de meg rundt og slo mot fotsålene mine, sier han.

Les også



– Svenske journalister i Etiopia holdt på å bli skutt

De to svenske journalistene som ble tatt til fange i Etiopia, skal nesten ha blitt skutt av soldater, ifølge Sveriges ambassadør til landet.
Flere beskriver å ha blitt dynket med iskaldt vann og hengt med hendene i taket slik at kun tåspissene nådde gulvet. Human Rights Watch og andre menneskerettighetsorganisasjoner har ikke tilgang til fengselet, men har sjekket de innsattes historier opp mot hverandre for verifisering.

Politisk styrt rettsvesen

Etiopias regjeringsparti – Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) – har styrt landet i over 20 år. Etter det omstridte valget i 2005, har myndighetene slått knallhardt ned på opposisjon og dissens.
Anti-terrorlovene fra 2009 er blitt brukt til å fengsle både journalister og opposisjonelle.
Samtidig som menneskerettighetssituasjonen i landet er blitt vanskeligere de siste årene, har landet hatt en stabil, økonomisk vekst i mange år.
Landets nå avdøde statsminister Meles Zenawi hadde et godt forhold til vestlige ledere, blant annet den norske regjeringen. Etiopia fikk i 2012 228 millioner kroner i bistand fra Norge.
Den siste rapporten forholdene på politistasjonen i Addis Abeba står i grell kontrast til beskrivelser av Etiopia som løfter millioner ut av fattigdom. Etiopias rettssystem er ikke uavhengig av regjeringspartiet, noe som blir ekstra tydelig i behandlingen av politiske fanger.
Torturen har ofte til hensikt å få fanger til å signere forklaringer og falske tilståelser. Blant fangene som ble bedt om å signere slike papirer var de svenske journalistene Johan Persson og Martin Schibbye som satt fengslet i det beryktede fengselet i 2011.

onsdag 16. oktober 2013

Africa’s journalists honor jailed editor Woubshet Taye


By Sue Valentine/CPJ Africa Program Coordinator
122
Woubshet Taye’s wife Berhane Tesfaye and their son accepted an award on behalf of the imprisoned journalist. (CPJ/Sue Valentine)
Journalists and media owners across Africa gave Ethiopian journalist Woubshet Taye a standing ovation in Cape Town on Saturday night at the CNN MultiChoice African Journalist Awards 2013, but he wasn’t there to see it. Instead his wife and son accepted the Free Press Award on his behalf.
Part of the citation for the award reads: “Ethiopia is a jewel in the African crown for its beauty, its people, its history and, most recently, for its astonishing growth rates. It is the judges’ view that journalists like Woubshet Taye and his colleagues Reeyot Alemu and Eskinder Nega should be out of prison and working to build the prosperity and the freedom of a new Ethiopia. The judges make this award in recognition of Mr. Taye’s work and in solidarity with his condition.”
Presenting the award to Berhane Tesfaye and the couple’s not-quite-five-year-old son, who were dressed in matching white and blue outfits, chair of the judging panel and editor-in-chief of the South African weekly City Press Ferial Haffajee said it was disappointing that “once again there were too many cases” for the judges to consider in this category, which recognizes “excellence and provides support to African journalists who report at continuing risk to their lives and safety.”
Woubshet, deputy editor of the Awramba Times, has been in jail for more than two years. He was detained in June 2011and held incommunicado before being convicted on terrorism charges and sentenced to 14 years imprisonment in January 2012. After Woubshet’s arrest, the paper stopped publishing in Ethiopia and the editor fled into exile. Accepting the award on his behalf, Berhane Tesfaye said her husband was grateful for the solidarity and received the award in the name of all journalists who are oppressed.
In April this year, Ethiopian authorities moved Woubshet to the remote Ziway prison about 83 miles (160 kilometers) from the capital Addis Ababa. His wife said that although it is a long way to travel, she is usually able to visit her husband every two weeks. However, she said that Woubshet’s parents–his father is 102 and his mother 90–are too old to make the journey. In September, Woubshet’s application for a presidential pardon was rejected, according to news sources.
The CNN MultiChoice African Journalist Awards began in 1995. A panel of 10 independent judges selected finalists and winners in 14 categories before naming an overall 2013 winner.
[Reporting from Cape Town]

A LOOK AT ETHIOPIA AFTER MELES ZENAWI| SWEDISH MEGAZINE

A LOOK AT ETHIOPIA AFTER MELES ZENAWI| SWEDISH MEGAZINE

220px-Meles_Zenawi_-_World_Economic_Forum_Annual_Meeting_2012
October 15th, 2013 -
When Meles Zenawi died a year ago, many people hoped for a liberalization of state control in Ethiopia, while others feared bloody power struggles and revolts.
Both hopes and fears came to naught. A new Prime Minister was appointed, with roots in the southern region. The same ruling group retained control of Ethiopia and many say: “Meles still rules.”
There is no tradition of democracy in Ethiopia, the authoritarian patterns are deeply rooted and the country has experienced only short spells of freedom to debate and criticize.
A divided opposition has been easy for Ethiopian security services to handle. Trying to quell a third of the population who feel their religion is oppressed can prove a lot more difficult.
Prime Minister of Ethiopia Meles Zenawi died a year ago. He led the armed uprising that toppled the military dictatorship in 1991. For 20 years, he cemented his power in Africa’s second most populous country. When Meles died, many people hoped for a liberalization of state control in Ethiopia, while others feared bloody power struggles and revolts.
Both hopes and fears came to naught. What happened, on the surface, was that a new Prime Minister was appointed − Hailemariam Desalegn − with roots in the southern region. The same ruling group retained control of Ethiopia and many say: “Meles still rules.”
In June, the opposition held demonstrations that were not put down brutally. This brought hope and led to new manifestations − where demonstrators were reportedly arrested and killed. Ethiopia’s development agenda is defended with harshness. Neither critical journalism or demands for more religious freedom by Muslims, nor nomadic groups’ claims for a reasonable pace of life changes are really listened to.
There is no tradition of democracy in Ethiopia, the authoritarian patterns are deeply rooted and the country has experienced only short spells of freedom to debate and criticize.
Ethiopia is composed of a large number of ethnic groups. Soon after taking power, the governing coalition party EPRDF instituted a federal reform. The regional administrative divisions aimed at developing the whole country but it has not led to significantly greater devolution and control over resources.
Meles was Tigrean. This ethnic group represents only 8 per cent of the approximately 85 million Ethiopians but the Tigrean Peoples’ Liberation Front TPLF led the overthrow of the military dictatorship in coalition with three other parties. The military and security services are dominated by Tigreans.
It is easy to imagine that the fragmentation and division could have disastrous consequences. Eritrea’s liberation was preceded by 30 years of bloody struggle, followed by a devastating − for both sides − war in 1998 and continued tensions affecting the entire development of the Horn of Africa.
Ethiopia has for several years enjoyed impressive economic growth. The education and health services are being expanded and many curves point in the right direction. Massive housing construction projects are transforming cities, replacing corrugated sheet slums by flats.
But inflation is sky high. In the cities there are widespread discontent with the price hikes, unemployment, lack of opportunities and political repression.
Many people dream of leaving the country and everyone seems to have close relatives abroad. The political opposition is based in the U.S. Intellectuals and journalists flee the country to escape imprisonment. Countless young women are part of the so-called ‘maid trade’, working in households in various Arab countries.
The urban population has been favoured at the expense of the rural areas. Now this is being partly reversed. Market reforms and the introduction of new technologies have given farmers the tools to raise themselves out of poverty. In the past, a farmer had to sell to government agents, but now the producer can sell to anyone and use a cell phone to find out the prices in town.
Many are excited about the progress, despite Ethiopia’s rural areas being still very poor. Land is formally owned by the state and the uncertain land rights have discouraged farmers from investing. But farmers can now get legal titles to the land they farm. The roads are better and the products can be transported to market.
There is also a safety net in the form of food assistance from the government via donors if there is lack of food before harvest or during droughts.
There is a three–pronged strategy to accelerate Ethiopia’s development: (i) New hydropower projects to provide electricity for the rural areas and export earnings when excess electricity is sold abroad; (ii) Expanding manufacturing to produce goods hitherto imported as finished goods; ( iii ) Production of sugar, rice, soybeans and other crops in large plantations to turn Ethiopia’s large imports into even greater exports to a richer and fatter world.
The government has been blamed for extensive land-grabbing with displacement of nomads and poor peasants. It is understandable that Ethiopia would like to use the sparsely populated lowland areas to increase growth and exports and create jobs for a growing population.
The scheme intends to create irrigation systems that benefit the farmers. Roads and schools will be built. There will be development. The lease is very cheap but the government is supposed to set conditions for investors to ensure wider development impact.
People move to new villages with schools and clinics. The government claims that this is voluntary, but human rights organizations have testified about forced displacement when land is being developed.
There is no empty land and the record-breaking land-leasing to domestic and foreign investors for commercial agriculture threatens to destroy traditional ways of life and wildlife habitat. There has been a veritable scramble for land in Ethiopia. Still the positive results have not been seen.
Hydropower is an important driving force for the development the Ethiopian government wants to achieve. An enthusiastic expert advisor highlights: “The rivers start flowing in this country. We must be able to make use of them ”
It is not as obvious as it sounds. Egypt wants exclusive rights to the Nile waters. Ethiopia’s construction of the big dam on the Blue Nile has been dogged by conflict-ridden negotiations with the downstream neighbours Egypt and Sudan. But Egypt is now weakened by domestic crises and Sudan has just been divided into two countries. Ethiopia is accelerating construction.
The Ethiopian government is negative towards civil society organizations working on human rights issues. Foreign-funded organizations grew up like mushrooms after the fall of the military dictatorship. In 2009 a law was passed that banned groups working on human rights to receive more than 10 per cent of their financing from abroad. There was an outcry. But the government had decided: foreign money should not influence policy.
Civil society is thus depressed. The political opposition is mostly in prison or in exile. Terrorist laws introduced in 2009 are used arbitrarily to detain people. Journalists and opposition take big risks. Bloggers write critically. However, security is effective. In the 80s when I lived in Addis, it was the East Germans who helped with the mind control. Now it is the Chinese.
Critical websites are blocked at a brisk pace, new ones opened just as fast. But there is opposition from a new perspective. About a third of the inhabitants of this country with a long Christian history are Muslims. There is a pride in that the groups have co-existed peacefully.
But now there is growing discontent among Muslims who accuse the government of interfering in the internal religious questions. This contradicts the country’s constitution which guarantees freedom of religion. Muslim groups have for nearly two years conducted peaceful protests outside mosques. The government has in some cases responded with violence and 29 Muslim leaders are detained under terror laws.
The threat of real terrorism is quite realistic in Ethiopia which is allied with the United States, has a military and political key role in the Horn of Africa and has troops fighting Al Qaeda-allied al Shabaab in Somalia. But the authorities’ heavy-handedness against peaceful religious practices may well contribute to a political radicalization of the protests.
A divided opposition has been easy for Ethiopian security services to handle. Trying to quell a third of the population who feel their religion is oppressed can prove a lot more difficult. (By Cecilia Bäcklander)
*********
Source: October 2013 issue of Sida’s magazine Omvärlden via Nordic Africa Development Policy Forum

mandag 14. oktober 2013

ስብሃት ነጋን አጅበው አክቲቪስት መስፍን ላይ ድብደባ የፈጸሙት ግለሰቦች ማንነት ታወቀ



Monday, October 14, 2013


(ዘ-ሐበሻ) በትናንትናው ዕለት ዘ-ሐበሻ በሰበር ዜና ባቀረበቸው ቪድዮ ላይ አክቲቪስት መስፍንን በቡጢ የተማቱትና የቆሙ መኪናዎችን ገጭተው ያመለጡት ግለሰቦች ማንነትን ጋዜጠኛ ኢየሩሳሌም አረአያ ማወቁን ለዘ-ሐበሻ በላከው መረጃ አስታወቀ፡፡
የሕወሓት መንደርን ከቃረምኩት በሚል በኢትኦጵ ጋዜጣ ላይ የሕወሓት ምስጢሮችን በሚያጋልጠው ጽሁፎቹ ታዋቂነትን ያተረፈው ጋዜጠኛ አረአያ ተስፋማርያም (ኢየሩሳሌም አረአያ) በትናንትናው እለት በአክቲቪስቱ ላይ ድብደባ የፈጸሙትን በሕግ የሚጠየቁት ግለሰቦች ሶስቱም የሕወሓት አባላት መሆናቸውን ጠቅሶ ማንነታቸውን ዘርዝሯል።

1ኛው. የሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ወንድም ታምራት ገ/መድህን፣
2ኛው. የወያኔ ኪነት አባልና ጊታሪስት ወዲ ሰቦቃ (በአሜሪካ ፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀ)፣                   

ስብሃት ነጋ
3ኛው ሃይሌ በአሜሪካ – የኢትዮጲያ ኤምባሲ የብርሃነ ገ/ክርስቶስ ሹፌር የነበረና በአሁኑ ወቅት በቪዛ ክፍል የሚሰራ ናቸው።
አክቲቪስት መስፍን ለደረሰበት ድብደባ ሕክምና የተከታተለ ሲሆን ጉዳዩን በሕግ እንደሚጠይቅ አስታውቋል። በሌላ በኩል የኢሳት ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን አንድ የቨርጂኒያ ጠበቃ አነጋግሮ ባቀረበው ዘገባው ስብሃት ነጋን ጨምሮ እነዚህ ግለሰቦች ሰውን በመደብደብና የሰው መኪና ገጭቶ በማምለጥ ወንጀሎች ከተከሰሱና ፍርድቤትም ጥፋተኛ ካላቸው በ እያንዳዱ ክስ እስከ አንድ አመት የሚያስቀጣ ቅጣት ሊጣልባቸው ይችላል። ስብሃት ነጋም የወንጀል ተባባሪ፣ እንዲሁም የሰው መኪና ገጭቶ ባመለጠ መኪና ውስጥ በመሄዳቸውና ወንጀልን በመተባበር ክስ በአሜሪካ ህግ በወንጀል ተባባሪነት ሊከሰሱ የሚችሉበት ህግ አለ።

søndag 13. oktober 2013

ETV በቦሌ አዲስ አበባ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን ዘገበ


ዘገባው የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የተቀነባበረ ይሁን አይሁን በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠ የETV ዘገባ እንደወረደ አቅርቤዋለው
እሁድ 3 2006 ዓም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የቤት ቁጥር 2333 ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ሁለት ግለሰቦች ተከራይተው በሚኖሩበት ቤት ውስጥ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ ጸረ ሽብር ሀይል ገለጸ፡፡
በፈንጂ ፍንዳታው ሁለቱ ግለሰቦች ህይወታቸው አልፏል፡፡
ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን የገለጸው ግብረሀይሉ በምርመራ የደረሰበትን ውጤትም በቅርቡ ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል፡፡
ህብረተሰቡ ቤት እና መኪናዎችን በሚያከራይበት ወቅት የተከራዮችን ማንነት ከማወቁም ባሻገር ለፖሊስ እና ለጸጥታ ሀይሎች ማሳወቅ እንዳለበት ግብረሀይሉ አሳስቧል፡፡

ስብሃት ነጋ ወንጀል ፈፀሙ፤ በአሁን ሰአት በፖሊስ እየታደኑ ነው

October 13, 2013

ከኢየሩሳሌም አርአያ
በአሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ከአንድ ሰአት በፊት ስብሃት ነጋና አብሯቸው የነበረ ግለሰብ በአንድ ኢትዮጲያዊ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ፈፅመው ማምለጣቸውን ማረጋገጥ ተችሏል። መስፍንsebehat nega one of the founders of TPLF የተባለው ኢትዮጲያዊ በአሁኑ ሰአት በሆስፒታል የሚገኝ ሲሆን የሲቪሊቲ ሩም ፓልቶክ አዘጋጅ አባ መላ በስልክ አግኝቶት ስለሁኔታው ያነጋገረው ሲሆን፤ መስፍን እንደገለፀው በድብደባው ጅርባው እንደተጎዳና ብዙ ደም እንደፈሰሰው ገፆዋል። እነስብሃት ድብደባውን ሲፈፅሙ በቅርብ ርቀት ቪዲዮ እየተቀረፁ እንደነበረና ይህኑን ማስረጃ ለፖሊስ መስጠታቸው ታውቋል። ድርጊቱ ከተፈፀመ በኋላ ፖሊስ በአካባቢው ፈጥኖ የደረሰ ሲሆን፣ በአሁን ሰአት እነስብሃትን ለመያዝ ፖሊስ መሰማራቱ ታውቋል።
posted mandefro mengistu

ይድረስ ለፕሬዚደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ


October 10, 2013
ይሄይስ አእምሮ
ክቡር ፕሬዚደንት ግርማ ሆይ፣
ኢትዮጵያንና “ሕዝቦቿ”ን የሚወዱ ከሆነ ቀጥዬ የምነግርዎትን ከልብ እንዲሰሙኝ በሚያምኑት እለምነዎታለሁ፡፡
ሰሞኑን በጡረታ ሊሰናበቱ እንደሆነ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዜና ዘገባ ሰማሁ፡፡ በመጀመሪያ ሥራዎን ጨርሰው ለዚህ በመብቃትዎ እንኳን ደስ ያለዎ፡፡ ቀጥዬም በሥራ ዘመንዎ ምን እንደሠሩና እኛ በምናውቅልዎም ሆነ እርስዎ በሚያውቋቸው ምክንያቶች የተነሣ ምን ምን መሥራት ፈልገው ሊሠሩ እንዳልቻሉ “ፕሬዚደንታዊ የሥልጣን ዘመን”ዎን የኋሊዮሽ በማሰብ  ከራስዎ ጋር በምልሰት ለመነጋገር የሚያስችል የማሰላሰያ ጊዜ በማግኘትዎ አሁንም በድጋሚ እንኳን ደስ ያለዎ – መልካም ዕረፍት፡፡ ነገር ግን ከስንብትዎ ጋር በተያያዘ የሰማሁት፣ ክፉኛ ያስደነገጠኝና ማመንም ያቃተኝ አንድ ጉዳይ ስላለ ይህን ማስታወሻ ልጽፍልዎ ተገደድኩ፡፡ President Girma Wolde-Giorgis
ጡረታ ሲወጡ እንዲኖሩበት መንግሥት የተከራየልዎት ቤት በነዚሁ ሚዲያዎች እንደሰማሁት በርግጥም በወር ብር አራት መቶ ሺ ነው እንዴ???…(የመጀመሪያውና ባለ530 ሺው ቤት ምናልባትም “ስለተወደደ” ሊሆን ይችላል እንደተሰረዘ ሰምቻለሁ፡፡)
የሰማሁት ጉድ እውነት ከሆነ አሁኑኑ ተግባራዊ ሊያደርጉት የሚገባዎ አንድ ምክር ልለግሰዎ፡፡ ይህን የምለው በብዙ ምክንያቶች ነው፡፡ ዋናው ግን የራሴው ምክንያት ነው፡፡ ቤቴን ቢጎበኙ – እርግጠኛ ነኝ – “ይቅርብኝ በራሴው ቤት እኖራለሁ” ይላሉ፡፡
ውድ ፕሬዚደንት ግርማ፣
የኔ ደመወዝ ብር 4200 ነው፡፡ ተቆራርጦ በሚደርሰኝ ብር 3200 አካባቢ አራት ቤተሰቤን ከወር ወር ማድረስ እየተቸገርኩ ውጪ ሀገር ከሚኖሩ የቤተሰባችን አባላት የምደጎምበት ጊዜ እጅግ ብዙ ነው፡፡ ልጆቼን ከፍዬ ማስተማር ስላቃተኝ ውለው እንዲመጡልኝ ብቻ በመንግሥት ትምህርት ቤት አስገብቻቸዋለሁ፡፡ ወሮችን እንዴት እንደማጋጥማቸው እኔና አንድዬ ብቻ ነን የምናውቅ፡፡ በመላዋ ሀገራችን የተንሠራፋው የኑሮ ውድነት እንኳንስ ከእጅ ወደ አፍ ልንኖር ከፍለን በማንጨርሰው ዕዳ ውስጥ ተነክረንም እንኳን ከአነስተኛ የምግብ አቅርቦትና ከትራንስፖርት ያለፈ ለሌላ ነገር የምናውለው ገንዘብ ሊኖረን አልቻለም፡፡
እንግዲህ ልብ ያድርጉ፡፡ እኔ ሀገሬን ከ30 ዓመታት በላይ በቅንነት አገልግያለሁ፡፡ በትምህርት ረገድም እስከዚህ ባያኮራም ሁለተኛ ዲግሪ አለኝ፡፡ እኔ መኖር አቅቶኝ እንግዲህ ከኔ ደመወዝ በግብር መልክ ለመንግሥት ገቢ ከሚደረግ አነስተኛ የሀገር ሀብት ለእርስዎ የቤት ኪራይ ብቻ ብር አራት መቶ ሺህ ወጪ ሲደረግ ይታይዎት፤ ይህ ድርጊት የግፎች ሁሉ የበላይ ሊሆን የሚገባውና ማሰብ የሚችል ኢትዮጵያዊን ጭንቅላት ሊያፈነዳ የሚችል አስነዋሪ ተግባር ነው፡፡ መንግሥትዎ ይህን ሲያደርግ የራሱ ዓላማ ሊኖረው ይችላል፡፡ ዐብዶም ሆነ ሰክሮ ሊሆን ቢችልም እርስዎ ግን ኃላፊነት ስላለብዎ ይህን ነገር በጭራሽ መቀበል የለብዎትም፡፡ ቢቀበሉት – እግዚአብሔር ምሥክሬ ነው – ከሚጠቀሙበት ይልቅ ይጎዱበታል፤ በጊነስ ቡክ ኦፍ ሪከርድስ የድንቃድንቅ መጽሐፍም በግፈኝነት ይመዘገቡበታል፡፡ ገንዘቡ ትልቅ ሆኖ እንዳይመስልዎ – እኛ ሕዝቡና ሀገሪቱ ሙልጭ የወጣን ድሆች ስለሆን እንጂ፡፡
ልብ እንዲያደርጉልኝ የምፈልገው ሌላ ጉዳይ አለ፡፡ ይሄውም እኔ በወርኃዊ ገቢ ከሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን በእጅጉ የተሻልኩ መሆኔን እንዲረዱልኝና እኔ ‹ሀብታሙ› ዜጋ እንዲህ በመኖርና ባለመኖር መካከል ተሰንቅሬና የኗሪ አኗኗሪ ሆኜ እየተቸገርኩ ሳለሁ ሌላውና ወርኃዊ ገቢው አምስት መቶም የማይደርስና ምንም ገቢ የሌለውም ዜጋ እንዴት አፈር እየጋጠ እንደሚኖር ያስቡት – መቼም አንጎል አለዎ ብዬ አስባለሁ፡፡ በዚህች የመጨረሻ ድሃ ሀገር በግል ጥረታቸው ሀብታም ለሆኑና ጡረታ ለሚወጡ ፕሬዚደንት ይህን ያህል ወጪ ከሀገር ባዶ ካዝና እንዲወጣ ፈቃደኛ መሆን በምድር ባይሆን በሰማይ ያስጠይቃልና አፋጣኝ እርምጃ ወስደው ከሕዝብና ከታሪክ ፍርድ በቶሎ ያምልጡ – ጊዜ አለዎት፡፡ ለሀገር የምንቆረቆር ዜጎች ዛሬ ድምጻችን ባይሰማና ብንታፈን ነገ በምናስመዘግብብዎ ክስ በሥጋም ይሁን በነፍስ እንደሚጎዱ ከአሁኑ ይረዱትና ጤናማ ውሳኔ ይወስኑ፤ በኋላ ለከፍተኛ ፀፀት እንዳይዳረጉ በቅጡ እንዲያስቡበት እማጸንዎታለሁ፡፡ የወያኔው መንግሥት የሚያደርገውን አያውቅምና የሀገርን አነስተኛ ሀብት እያሟጠጠና እያነቀረ ለእንደዚህ ዓይነቱ አስገራሚ ወጪና ለጦር መሣሪያ ግዢ እንዲሁም ለወንበር ጥበቃ ለሚያሰማራቸው የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማትና ባልደረቦች ቢከሰክስ የሀገሪቱ ችግር ለሱ ጉዳዩ ባለመሆኑ የመንግሥትን “ችሮታ” ከቀጣይ የአብሮነት ሕይወታችን ለይተው እንዲመለከቱ አሳስብዎታለሁ፡፡ በምንም ይሁን በምን ያገለግሉት የነበረው መንግሥት ሀገሪቱን እንደሀገሩ የማያይ ባዕድ አገዛዝ በመሆኑ ለሀገሪቱና ለዜጎቿ ማሰብ አይችልም – ቢያስብ ኖሮ የሦስት መቶ ብር ደመወዝተኛ ከጉሮሮው እየተነጠቀና በኑሮ ውድነትና በደመወዝ ማነስ ምክንያት በርሀብ አለንጋ እየተገረፈ የወር ደሞዙን ለአባይ ግድብ እንዲሰጥ በሚገደድበት በዚህ አስቸጋሪ የድህነት ዘመን ግፋ ቢል ከአሥርና አሥራ አምስት ሺህ ብር ባለፈ ይህን ያህል ገንዘብ ለኪራይ ብቻ ባልመደበ ነበር – ስለዚህ ዋናው ኃላፊነት የእርስዎ እንጂ የዕብዱ መንግሥት እንዳልሆነ ልጠቁም እፈልጋለሁ፡፡ ገበሬው በርሀብና በርዛት እየተሰቃዬና ባገኘው አቅጣጫ እየተሰደደ፣ የሠራተኛው ደመወዝ ለወር ቀርቶ ለሦስትና አራት ቀናትም እንኳ መሆን አቅቶት ብዙው ሰው ከመደበኛ ሥራው በተደራቢ በልመና ኑሮውን ሊደጉም እየተገደደና ሀገሪቱ በድህነት ሰንጠረዥ በመጨረሻው ተርታ ተቀምጣ እያለ እርስዎ በወር ይህን ያህል ገንዘብ በሚከፈልበት ቤት ውስጥ ለመኖር ቢስማሙ የኢትዮጵያ አምላክ አይለመንዎት፤ ይህን ተማፅኖየን እምቢ ቢሉ ፈጣሪ የሲዖል ወራሽ እንዲያደርግዎ የዘወትር ጸሎቴ ይሆናል፡፡ የዚህ ቤት ባለቤት ቢፈተሸ ምናልባት ከወያኔዎቹ አንዱ እንደሚሆን አልጠራጠርም – በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ለመምታት፡፡ ቤቱ የማንም ይሁን የማን -  ነገር ግን እርስዎን በጭራሽ አይመጥንምና – የሕዝብ አፍም በሥጋም በመንፈስም እያሳደደ ዕረፍት ይነሳዎታልና – ወደፊትም እርስዎ ወይም ልጆችዎና የልጅ ልጆችዎ ዕዳዎትን ለመክፈል ለፍርድ ይቀርቡበታልና ይቅርብዎ፡፡ ከኔ አወረድኩ፤ቀሪው የእርስዎ ነው፡፡
posted ማንደፍሮ መንግስቱ

lørdag 12. oktober 2013

በወያኔው ብአዴን ውጥረት የነገሰበት ግምገማ ከ 170 በላይ አባላት በአንድ ጊዜ መልቀቂያ እንዳስገቡ ተጠቆመ


33
ሁልጊዜም በያመቱ የአባላት ግምገማ (በሂሳብ ሰዎች አጠራር የሰዎች ኢንቬንተሪ) የሚያካሂደው ፋሽስት ወያኔ፤ የታመመ፣ የደከመ፣ ተነሳሽነት የጎደለው እንዲሁም ሌላል ሌላም በሚል ሰበብ፤ የፖለቲካ አቋም መስመራቸውን ያላስተካከሉ የሚላቸውን እንደሚቀጣ ይታወቃል። በዚህ መሰረትም ብአዴን የሚባለው የወያኔው አንዱ አንጃ ኪራይ ሰብሳቢነት በሚል አጀንዳ የጀመረው ግምገማ ከፍተኛ ውዝግብና መተረማመስ ከመፍጠሩም በላይ በስብሰባው የተገኙ አባላት በብአዴንና በወያኔው አገዛዝ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ በማሰማት ላይ መሆናቸው ታውቋል።
“ባይናችን እያየነውና እየሰማነው ካለው በአገዛዙ ሹመኞች የሚከወን ንቅዘት አንጻር እኛን እስክርቢቶ ወሰዳችሁ እያሉ መገምገም ፌዝ ነው” ያሉት የግምገማው ተሳታፊዎች “በሚሊዮን ዶላር በሚቆጠር መጠን ወደ ውጭ ሀገራት ባንኮች የሚወጣውን ሃብት መቆጣጠር የተሻለ ነበር” ሲሉ በምሬት ተናግረዋል። አክለውም “ልጆቻችንን በቅጡ ለመመገብና ለማሳደግ ካቃተን አባላት ላይ የአባልነት ክፍያ እያለችሁ ትሰበስባላችሁ ሌላው ግን አገዛዙ የቸረውን የአገዛዝ ቦታ ተጠቅሞ ከሕዝብ በዘረፈው ሃብት ሶስትና አራት ሕንጻዎችን ሲገነባ የሚናገረው የለም፤ እኛም መረረን መኖር አቃተን በዚሁ ሳቢያም አባላት መልቀቂያ እያስገቡ ነው ብለዋል።”

ከ15 ሺ በላይ የኢህአዴግ አባላት መልቀቂያ አስገቡ



ጥቅምት (አንድ)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ እያካሄደ ባለው የአባላት ግምገማ ወቅት ከ15 ሺ በላይ አባላት በአንድ ጊዜ መልቀቂያ ማስገባታቸው ይፋ ተደርጓል።

ስራቸውን ከሚለቁበት ምክንያቶች መካከል  በድርጅቱ አመኔታ ማጣት ፣ ተገቢውን አገልግሎት ክፍያ አለማግኘት፣ ለድርጅቱ የሚከፍሉት ገንዘብ ከፍተኛ መሆን እና የድርጅቱ አባላት ሹመት በወገን መሆኑ የሚሉት ተጠቅሰዋል።
ከፍተኛ የአባላት መልቀቂአ ቁጥር ከተመዘገበባቸው ክልሎች መካከል ኦሮሚያ በ9 ሺ 4 መቶ 56 አንደኛ ሲሆን ፣ አማራ፣ ደቡብ ክልል እና ትግራይ በተከታታይ ያሉትን ደረጃዎች ይዘዋል። በትግራይ በ2005 ዓ/ም 1 ሺ 1 መቶ 13 ሰዎች የህወሀት አባላት መልቀቂያ አስገብተዋል።
ኢህአዴግ 5 ሚሊዮን አባላት እንዳሉት ቢነገርም ፣ በንቃት የሚሳተፉት 2 ሚሊዮነቹ ብቻ ናቸው ተንብሎአል። ከእነዚህ መካከል 20 ሺ የሚሆኑት በስም ብቻ አባላት ተብለው ቢመዘገቡም፣ በአካል የሌሉ መሆናቸውም ተገልጿል።
በስብሰባው አብዛኞቹ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለደሞዝና ለስራ ሲሉ አባል እንደሚሆኑ የተገለጸ ቢሆንም በአለፉት አመታት ድርጅቱን ከተቀላቀሉት ተማሪዎች መካከል ስራ አገኙት ሩብ አይሆንም ተብሎአል።
በክልል ዋና ዋና ከተሞች በአዋሳ፣ ባህርዳር፣ እና መቀሌ ውጤት ያላቸው ተመራቂዎች ስራ ሳይዙ፣ ውጤት የሌላቸው የድርጅቱ ነባር አባላት በተቃራኒው ስራ መቀጠራቸው በአባላቱ ላይ ቅርታ እንዲፈጠር አድርጎአል ተብሏልም ።
ዛሬ ስራ ማግኘት የህልም እንጀራ ነው ያሉት አባሎች፣ ዲግሪ ይዘው ስራ ለማግኘት ከሶስት እስከ 4 አመታት የሚጠብቁ ተመራቂዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
ኢህአዴግ መልቀቂያ ያቀረቡ አባላቱን ጥገኞች ሲል ሰይሞአቸዋል። የድርጅቱ አባላት ለኢሳት እንደገለጹት አብዛኞቹ የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች በሙስና የተዘፈቁ ናቸው። ኢሳት በሚቀጥለው ሳምንት <<የድርጅት አባላት እንዲያውቁት>> በሚል የብአዴን የአመራር አባላት ሙስናን በተመለከተ የላኩትን ደብዳቤ ይፋ እንደሚያደርግ ለመግለጽ ይወዳል።
በተመሳሳይ ዜናም አክራሪነትና ጽንፈኝነትን አስመልክቶ ስልጠና ለመስጥት የፈዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሐረማያ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር ትናንት ያደረገዉ ስብሰባ ያለዉጤት ተበትኗል።
መንግስት ንጹሀንን ያለምንም መረጋገጫ አክራሪ አሸባሪ ብሎ መፈረጁ ግዜ ያለፈበት ነው”ያሉት የስብሰባው ተሳታፊዎች፤”በመንግስት እየተባለ ያለውን ነገር+ እንኳን  የዩንቨርስቲዉ ማህበረሰብ ፤ሳይማሩ እያስተማሩ ያሉት እናት አባቶቻችንም አይቀበሉትም “ብለዋል።
ተማሪዎችና መምህራን  በማከልም፦”የመረጃ ምንጫችን ኢቲቪ ብቻ ነው ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችሗል” በማለት  የመንግስት ባለስልጣናትን ሞግተዋቸዋል።
“ጽንፈኛ” የሚለዉ ቃል በባርያ ፍንገላ ግዜ በባሪያ አሳዳሪዎች ላይ ያምጹ ለነበሩ ግለሰቦች የተሰጠ ስያሜ ነው በማለት የተናገሩት  አንድ ክርስቲያን የሆኑ የስብሰባው ታዳሚ፤ “መንግስት የእስልምና ሐማኖት ተከታዮች  በክርስቲያኑ ላይ ጦርነት ሊያዉጁ ነው ብሎ ቢናገር ፤ህዝበ ክርስቲያኑ አይቀበለውም”ብለዋል።
ግለሰቡ አስተያየታቸውን ሲያጠቃልሉም፦ኢትዮጵያ ዉስጥ አክራሪ አለ ማለቱ አለማቀፋዊ እዉቅናን ያላገንኘና ተዓማኒት የሌለዉ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ቢ.ቢ.ኤን ዘገባ፤በስብሰባው ላይ በዩንቨርሲቲዉ ሶላትና ሂጃብን አስመልክቶ እገዳ ለማድረግ እቅድ እንዳለ የቀረበው ሃሳብ በሁሉም ተሳታፊዎች ከፍ ያለ ተቃውሞ ገጥሞታል።
“ኢትዮጵያን ልክ እንደ አፍጋኒስታንንና ፓኪስታን ችግር ያለባት ማስመሰሉ ተገቢ አይደለም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ተቻችሎ ያለ በመሆኑ ያንዱ ወገን ሐይማኖት መከበር ለሌላዉ ስጋት አይደለም፤”ያሉት ተሳታፊዎቹ፤ ሰዎችአለባበሳቸዉን ከቀየሩ አመለካከታቸዉን ይቀይራሉ ማለቱ  ስህተት ስለሆነ “ሀይማኖታዊ አለባበስ ከዩኒቨርሲቲ በር መልስ”የሚለው ሃሳብና እቅድ ተቀባይነት የለውም”ብለዋል።
የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር  በሐረማያ ዩኒቨርስቲ” አክራሪነትንና አሸባሪነትን” አስመልክቶ ባዘጋጀዉ በዚህ  ስልጠና ላይ እስከ አስራ ሁለት ሺ የሚጠጉ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
ይሁንና በርካታ ተማሪዎች የመንግስት ባለስልጣናት የሚያቀርቡትን ሐሳብ ፊት ለፊት በንግግር ከመቃወማቸውም በላይ   ስብሰባዉን ረግጦ ወጥተዋል።
በማንደፍሮ መንግስቱ